IRROB.ORG

Home » News » Charity » Breaking News from warring Tigray

Breaking News from warring Tigray

የትግራይ መከላከያ ሰራዊት እና ምሊሻ በትላንትናው እለት እጅግ በጣም ብዙ ጀብዶችን ሲፈፅም ዉለዋል።

1. ከኮረም ወደ ማይጨው በሚወስደው መንገድ ላይ ሕጉምብርዳ በምትባል ቦታ ላይ ጠላት በ25 አውቶቡሶች ተጭኖ ወደ ግዳጅ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ ፤ የትግራይ መከላከያ ሰራዊት በወሰደው ድንገተኛ ጥቃት ጠላት ከአውቶቡስ ሳይወጡ እዛው እያሉ 23ቱ አውቶቡሶች ዉስጥ እንዳሉ ተቃጥለው የተደመሰሱ ሲሆኑ። የቀሩት 2ት አውቡሶች ላይ የነበረው ጠላት ፤ ከ አውቶቡስ ወጥተው ለመሸሽ ሲሞኩሩ አንድ በአንድ ተለቅመው መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

2. የውቅሮ ወጣቶች ጀግንነታቸው ተነግሮ የሚያልቅ አይደለም። ትላንት ጠላት በተሰበሰበበት በውቅሮ ማሰራጫ ማእከል ላይ ፤ አጭር ኦፖሬሽን በመስራት እዛው በተሰበሰቡበት መደምሰስ ችሏል።

የዛሬ ከገረመኝ የትግራይ ምልሻ ጀብድ ደሞ፤ እንደ አሸን የጎረፈው ተጨማሪ እግረኛ ሃይል በዓፋር በኩል ሲገቡ የነበሩት የመሽረፈት እና የኢሳያስ ወታደሮች ፤ በእግራቸው ረዥም ሰልፍ ይዘው የትግራይ መከላከያ ሰራዊት አሉበት ወደሚባለው ቦታ ሲጓዙ የነበሩት በቁጥር ወደ 9000 የሚሆኑ ምሊሻው ምሽግ ይዘው በድንገት ሲያጠቁ አብዛኛው እዛው ሲገደሉ የተቀሩት ምርኮኛ ሁነዋል።

ትግራይ የገባ ጠላት እዛው እንደሚቀበር የገባቸው አለቆቻቸው እና አዛዦቻቸው፤ ትግራይ ሳይገቡ ዓፋር ሁነው ገባ በለው እያሉ እያስጨረሱዋቸው መሆኑን የተማረኩት ተናግረዋል።

%d bloggers like this: